በአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ኢስዋቲኒን 4 ለ1 በሆነ ድምር ውጤት በማሸነፍ ከ18 ዓመታት በኋላ ኤርትራን ወደ አፍሪካ ዋንጫ የምድብ የማጣሪያ ውድድር ካበቁት ተጫዋቾች መካከል ሰባቱ ወደ አገራቸው አለመመሳቸውን ምንጮች ለቢቢሲ አረጋገጡ። በቅድመ ማጣሪያው ሁለት ዙር ጨዋታ ከተሳተፉት የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን አባላት መካከል አስሩ ከአገር ውስጥ የተመረጡ ተጫዋቾች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 14ቱ ደግሞ በባሕር ማዶ የሚኖሩ ኤርትራውያን ናቸው።
ከአገር ውስጥ ከተመረጡት ከተመረጡት አስር ተጫዋቾች መካከል ከውድድሩ በኋላ ሰባቱ ወደ አገራቸው አለመመለሳቸውን ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል። ከ18 ዓመታት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ድልድል የተመለሰው የኤርትራ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን በሁለት ዙር ደቡብ አፍሪካዊቷ አገር ኢስዋቲኒን (የቀድሞዋ ስዋዚላንድ) በመግጠም ነው በሁለቱም ጨዋታ ለማሸነፍ የቻለው።
Matchday Refresh
A cool banner-style placement for sponsors — perfect for matchweek campaigns.
የኤርትራ ብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያውን ዙር ጨዋታ በደጋፊዎቹ ፊት በአገር ውስጥ በዋና ከተማዋ አሥመራ መጫወት የነበረበት ቢሆንም ጨዋታው የተካሄደው ግን በሦስተኛ አገር ወስጥ ነበር። ቡድኑ በአሥመራ ስላልተጫወተበት ምክንያት ይፋዊ ምክንያት ባይገለጽም በኤርትራ ውስጥ የሚገኙ ስታዲየሞች ከአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ደረጃ በታች በመሆናቸው እንደሆነ ግን ሲነገር ቆይቷል።
የቀይ ባሕር ግመሎች በመባል ከሚታወቁት የኤርትራ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን አባላት መካከል አብዛኞቹ ወደ አገራቸው አልተመለሱም። ከአስሩ ተጫዋቾች መካከልም ሦስቱ እነሱም የቡድኑ አምበል አብለሎም ተክለዝጊ፣ የመሀል ሜዳ ተጫዋቹ ሄኖክ ታደሰ እና ሮሜል አብዱ ብቻ መመለሳቸውን ቢቢሲ ማረጋገጥ ችሏል።



